Entertainment  | Mutimedia | Educational
Welcome
Login / Register

News


  • ውቢት ኢትዮጵያ!

     

    የኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮሚሽን “የ13 ወር ፀጋ” በሚል ርዕስ ከሚያሳትማቸው ፖስተሮች የዝነኛዋ “ውቢት ኢትዮጵያ” አስደናቂ ተፈጥሮአዊ ውበትና ግርማ ሞገስ የታየበት ፖስተርዋ ሁሌ ከማይረሱን መሃል አንዳቸው ነው።

    የ4 ልጆች እናት የነበረችው ውቢት አመንሲሳ በወለጋ ክፍለ ሀገር ተወልዳ አድጋ ወደ አዲስ አበባ ተጉዛ እቴጌ መነን ትምህርት ቤት ተምራ ቦኋላ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮሚሽን ተቀጥራ ለመስራት አበቃች። ከልጆችዋና ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ተቀጥረው ይሰሩ ከነበረው ባለቤቷ ጋር አዲስ አበባ ትኖር ነበር። ከዚህ ቀደም የውቢት አመንሲሳ እውነተኛ ስሟ አልማዝ አመንሲሳ ነው ብለን ተናግረን ነበር፡ የተሳሳተ መረጃ በመልቀቃችን ይቅርታችሁን እንጠይቃለን። በቅርቡ እንደተረዳነው ግን አልማዝ አመንሲሳ በወቅቱ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተቀጥረው ይሰሩ የነበሩና ዛሬ ነዋሪነታቸው አሜሪካ የሆነው የውቢት ኢትዮጵያ እህት ናቸው። ከአልማዝ ጋር አብረው ይሰሩ የነበሩት የስራ ባልደረባቸው ልንረዳው እንደቻልነው ምስሉ ላይ ያለችው የአልማዝ እህት ውቢት አመንሲሳ ከቱሪዝም ስራዋ ውጭ ሞዴል ወይ የፊልም ተዋናይት አልነበረችም። 1970ዎቹ የብሄራዊ ቱሪዝም ኮሚሽን ለገቢ ማሰባሰብያ የሚሆኑ ድንቅ ድንቅ ፎቶዎችን አንስቶ ለመልቀቅ የፈለገበት ወቅት ነበር። ውቢት በቱሪዝም ኮሚሽን ፎቶ የመነሳት እድል አጋጥሟት ነው ለ <<ውቢት ኢትዮጵያ>>ነቷ ልታበቃ የቻለችው። ኩባዊ ኢትዮጵያዊው የታሪክ ምሁር ኤድዋርዶ ባይሮኖ እንዳስረዳን ውቢት አመንሲሳ ለፎቶዉ 5 ሳንቲም ሳትቀበል ፎቶዉ ያስገኘና እስከ ዛሬ እያመነጨ ያለው ገቢ ሙሉ ለሙሉ ለኮሚሽኑ እንዲረከብና የሃገራችን ቱሪዝምን እንዲያገለግል ፍላጎቷ ነበር።

    በ2000 ዓም ለህክምና ወደ አሜሪካ አምርታ ህዳር ወር 2001 ዓም ውቢት ኢትዮጵያ በሞት ተለየችን።

    መልከ መልካሟ ውቢት ኢትዮጵያ ሀገርዋን ላገለገለችበትና ስማችን ላስጠራችበት ምስጋናችን ይገባታል።

    ነፍስሽን በገነት ያኑረው <3 

    This is the famous image of "Woubit Ethiopia" as she was dubbed. This image was taken sometime in the late seventies by Ethiopia's tourist commission board. Not much is known about the woman subject of the photo.

    Her name is Woubit Amensisa. Hailing from Ethiopia's Wollega region, she later moved to Addis Ababa and was a student at Etege Menen School, before finishing her studies and getting a job with Ethiopia's tourism commission. She lived in Addis Ababa with her husband, who worked at Ethiopian Airlines, and her four children. A while ago we released this picture saying that her real name was Almaz Amensisa. We'd like to apologize for the error. The truth is, the beautiful woman in the picture is really named Woubit Amensisa, while Almaz Amensisa is her sister who worked for Ethiopian Television and now resides in the USA. Unlike what is widely believed, outside of her job at the national tourism commission, Woubit was neither a model nor an actress. Her colleagues at the national tourism office managed to convince her to take up a photo shoot opportunity at a time when the national tourism commission was collecting images to serve for promotional purposes. But her image became an international sensation. According to Cuban Ethiopian historian Eduardo Byrono, Woubit never asked for compensation for the photo and only wished that the income serve Ethiopia's tourism industry.

    In 2007, Woubit came to the USA to get treatment for an undisclosed illness. Sadly, in November of 2008, Woubit Ethiopia's health had declined and she passed away in the USA.

    Although every Ethiopian is familiar with the class, elegance and natural beauty she exhibits in this image, she didn't get the recognition she deserved in her lifetime.

    <3 Woubit Amensisa aka Woubit Ethiopia <3 , rest in eternal peace!

    To enlighten your fellow Ethiopian or anyone for that matter, like and share this pic!

    Read more »
  • Ancient city uncovered in Ethiopia | BBC News

    Ancient city uncovered in Ethiopia

    Farmers in the eastern Ethiopian city of Harlaa have long found strange objects on their land, including Chinese coins, prompting a local myth that the area was once home to giants.

    A team of archaeologists has now uncovered what they believe was an ancient city and trading hub dating as far back as the 10th Century, with artefacts from Egypt, India and China.

    Prof Timothy Insoll is one of the archaeologists who made the stunning discovery.

    Photo: An archaeologist at work at the site, Credit: Timothy Insoll

    Read more »
  • How to Be a Good Wife

    Being a good wife is not easy, even if you have a near-perfect husband. To be a good wife, you have to be able to communicate effectively, to keep your romance alive, and to be your husband's best friend while maintaining your own identity. If you want to know how to do it, just follow these steps. 

    1,Express your feelings and needs effectively. Your husband doesn't have clairvoyant powers. If you want something, ask. If something is wrong, say so. Don't drop hints or figure he'll "come around" or you'll never get anything done. If you want to be able to express how you feel, you should be able to speak with a positive tone and to listen to what your husband says instead of being accusatory. Here are some ways to do it:

    • Send "I messages." Instead of accusing him of not meeting your needs, focus the conversation on yourself. For instance, tell him, "I feel ignored when I don't see you until 6:30 every night."
    • Listen to what he says. When he tells you something, repeat what he said back to him so that he knows you understand. For example, "I hear you saying that you're worried about finances, and that's why you've been working late."
    • Avoid passing judgment. Let him finish what he's saying before you respond. After he's done talking, offer a solution. For instance, say, "I'm willing to live on a tighter budget if that means that I get to see you more often." 

    2,Pick your battles. Some issues are worth fighting about, and some aren't. If you spend all of your time nitpicking your husband about minor problems that don't really matter, then he's not going to listen to you when major issues come up.

    • Criticism can destroy a relationship. As long as the dishes are clean and unbroken, for instance, don't nag your husband about how to load the dishwasher "the right way." Let him do things his own way. Don't sweat the small stuff.
    • Avoid criticizing your husband without doing it constructively. Remember to try and be calm and rational, as strong emotions can easily turn a discussion into an argument. If you criticize every little thing he does, then he will quickly tune you out.
    • You should praise your husband for the things he does right much more than you argue with him about things that he does wrong. This will make him much more likely to listen to you, and much happier to be around you.

    3,Be understanding when you discuss an issue with your husband. Fight right. Don't let anger take over because it may cause you to say things that you will regret later. Even when you don't agree with your husband, you need to respect his opinion and his viewpoint. To be a good wife, you need to understand that you may never agree on certain issues. No couple has an identical set of morals and beliefs, which means that both of you will need to learn to cope with occasions where you just can't resolve your opinions.

    • Talk to him at the right time. Don't just spring your problems on him whenever. Avoid bringing up problems before dinner, while he's paying bills or when he's immersed in a stressful situation, like fixing a problem with your car. And never, ever start an argument in front of your children.[1]
    • When you're wrong, admit it. You need to learn to respond to arguments and remain rational so you can recognize and apologize when you've made a misstep.

    4,Talk to your husband, not about him. Never talk to your friends or your family and say negative things about your husband if you're not communicating with him first. Talking about your husband behind his back is disloyal. When you get married, your first loyalty is to your partner, not to your birth family or your social group.

    • Complaining about your husband to your friends and family will not only not solve any of your problems, but it will also make them view your relationship in a more negative light.
    • Your friends and family may think they know what's best for you, but they don't know your relationship as well as you do and may unintentionally give you bad advice.

    Read More

    .....................................

    Read more »
  • የወሎ ‹‹ላሊበላ›› ትንሣኤ

    በጥቂቱም ቢሆን ዕድሜ እየተጫጫናቸው መምጣቱ ከፊታቸውና ከመላ ሰውነታቸው ይነበባል፡፡ በተለይም ጣታቸው፣ እጃቸው፣ ክንዳቸውና ቀሪ ሰውነታቸው ጠንከርከር የሚለው መድረክ ላይ ወጥተው ማሲንቋቸውን ሲይዙ ነው፡፡

    የ72 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ የሆኑት አቶ አራጌ ኢማሙ በወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን ውስጥ ማሲንቆ ተጫዋች ሲሆኑ ከ23 ዓመታት በፊት የፈረሰው የቀድሞው ወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን ውስጥም ሙዚቀኛ ነበሩ፡፡

    አቶ አራጌ እንደሚናገሩት በ1960ዎቹ ‹‹የወሎ የሀገር ባህል ተጫዋቾች ክበብ›› በሚል የተመሠረተው ቡድን 97 አባላት ነበሩት፡፡ ‹‹መሬት ላራሹ›› ከታወጀ በኋላ የቡድኑ አባላት ወደ እርሻና ወደ ሌላም ሥራ ተሰማርተው ይበተኑና የአባላቱ ቁጥር ይቀንሳል፡፡ የቀሩት አባላት በቀለመወርቅ ደበበ ሥር ሆነው ወሎ ላሊበላ የኪነት ቡድን በሚል መንቀሳቀስ ይጀምራሉ፡፡

    የወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን በተነሳ ቁጥር ከአፍ የማትነጠለው ማሪቱ ለገሠን ጨምሮ ዝነኛዋ ዚነት ሙሀባ፣ ወርቅነሽ ተጫን፣ ፀሐይ አበራ፣ ዙሪያሽ አብዩ፣ ፀሐይ ካሳ፣ መሀመድ ይመርና ትግስት አባተጫን የመሳሰሉ የቡድኑ አባላትን በርካቶች ዛሬ ድረስ ያስታውሳሉ፡፡ የቡድኑ የቀድሞም የአሁንም አባል አቶ አራጌ ከማሲንቆ በተጨማሪ አኮርዲዮን መጫወትና ማንጎራጎር የሚሞክሩ ሲሆን፣ የያኔው የኪነቱ አባላት ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ አንስተው ያገኙት የነበረውን አነስተኛ ገንዘብ ሲያስታውሱ ይገረማሉ፡፡

    በርካታ አስተያየት ሰጪዎች በወቅቱ ጥራቱን የጠበቀ ዜማ፣ ግጥሙ ያማረና ባህልን ጠንቅቆ የተከተለ ሥራ የወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን ይሠራ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ በሐሳቡ የሚስማሙት አቶ አራጌ በተለይ በ1970ዎቹ መጀመሪያ ‹‹ፈጣኑ ባቡሩ›› እና ሌሎች በርካታ ተወዳጅ ዜማዎች እንደነበሯቸው ይናገራሉ፡፡ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ ላይ ‹‹ፈጣኑ ባቡሩን›› ተጫውተው በወቅቱ ከደርግ ሊቀመንበር ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም መጓጓዣ መኪና ማግኘታቸውን ያወሳሉ፡፡

    ወሎ ላሊበላ የኪነት ቡድን ከተበታተነ በኋላ የአብዛኞቹ ዕጣ ፈንታ እንደሆነው ሁሉ ራሳቸውን ለማስተዳደርና ቤተሰብ ለመደጎም በተለያየ አገር እየተዘዋወሩ ማሲንቆ ይጫወቱ ነበር፡፡ ዛሬ ባለትዳርና የስድስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ አራጌ ሙዚቃ በጀመሩበት ወቅት ሙያው ባይከበርም ለሙያው ያደረጉትን ጥረት ይናገራሉ፡፡ 

    ከቡድኑ ወጥተው ከገጠማቸው ውስጥ ያጫወቱን፣ በአንድ ወቅት ባለቤታቸው የነበሩት ሴት ልጅ ወልደው ይሞትባቸዋል፡፡ ልጁ ሲሞት የባለቤታቸው ቤተሰቦች ‹‹የላሊበላ ልጅ ምን ያደርግልሻል›› እያሉ ያጥላሏቸው ነበር፤ በዚህ የተነሳ ለፍቺ እንደተዳረጉም ይናገራሉ፡፡

    ‹‹በሙያው ስንናቅበት ኖረናል›› የሚሉት ሙዚቀኛው ዛሬ ላይ የተሻለ አመለካከት አለ ብለው ስለሚያምኑ ዳግም የወሎ ላሊበላ ቡድን አባል መሆናቸውን በበጎ ያዩታል፡፡ አቶ አራጌ የያኔው ቡድን ላይ የሚደርስ የለም ቢሉም፣ ምንም ቢሆን ደግሞ መሰባሰቡና የሙዚቃ ሕይወትን በኅብረት መግፋቱ መልካም ነው ባይ ናቸው፡፡ በቡድኑ ዳግም ዕድል ያገኙት ባለሙያው ሕይወቴ እስካለ ድረስ በቡድኑ ውስጥ እኖራለሁ ይላሉ፡፡

    ዛሬ ላይ ሆነው ወደ ኋላ ሃያ ሦስት ዓመታትን አሻግረው ሲመለከቱ፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ደማቅ አሻራ አሳርፎ፣ ተተኪን አፍርቶ ለመዝለቅ ይንደረደር የነበረው ታላቁ የወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን መበተኑን በርካቶች በቁጭት ይናገራሉ፡፡ 

    የወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን በደርግ ወቅት በተበረከተላቸው መኪና በመንቀሳቀስ የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ በተሰጣቸው ኃላፊነት በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረዋል፡፡ አገራዊ መልዕክት ካሏቸው ሙዚቃዎች በተጨማሪ ልዩ ልዩ ቅኔያዊ ትርጓሜ ያላቸው ሥራዎች ካበረከቱት የቡድኑ አባላት አንዳንዶቹ ጥላሁን ገሠሠና መሀሙድ አሕመድን የመሰሉ ሙዚቀኞች የነበሩበት የሕዝብ ለሕዝብ ቡድን አባላትም ነበሩ፡፡

    በርካታ ድምፃውያን፣ ተወዛዋዦችና የባህል ሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋቾች ያፈራው ይህ ቡድን ኢሕአዴግ ሲገባ አባላቱ ተበታትነው ገሚሱ በሙዚቃ ሕይወታቸው ሲቀጥሉ ቀሪው ወደ ሌላ ሕይወት ፊታቸውን አዙረዋል፡፡ የቡድኑ መፍረስ ዘወትር ይቆረቁራቸው የነበሩ አባላቱ በተለይም ቀድሞ በቡድኑ ከበሮ ተጫዋች የነበረው ዳምጤ መኰንን (ባቢ) ከረዥም ጊዜ ጥረት በኋላ በምሥራቅ አማራ ያሉ ወጣቶችን መልምለውና ከቀድሞ ቡድን ጥቂት አባላት አክለው ዳግም በኅብረት እንቅስቃሴ ጀምረዋል፡፡

    ይህ የወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን በአዲስ አወቃቀር ከተቋቋመ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ የተመለመሉት ወጣቶች ለስድስት ወር ያህል በወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮምቦልቻ ካምፓስ ውስጥ ሥልጠና ከተሰጣቸው በኋላ መስከረም 14 ቀን 2006 ዓ.ም. ቡድኑ በይፋ ተመርቆ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ቡድኑ ደሴ ውስጥ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ በተጨማሪ በተለያዩ አገሮች እየተዘዋወረ ሙዚቃና ውዝዋዜ አጣምሮ ያቀርባል፡፡ ቡድኑ ባለፈው ጥር ወር በተካሄደው 4ኛው የባህል ፌስቲቫል ላይ ክልሉን ወክሎም ቀርቦ ነበር፡፡ 

    ከዓመታት በኋላ ዳግም የተነሳው ቡድኑ ድምፃውያን፣ ባህላዊ ሙዚቃ  መሣሪያ ተጫዋቾችና ተወዛዋዦችን አጣምሮ 34 አባላት የያዘ ሲሆን፣ በርከት ያሉ ብሔር ብሔረሰቦችን ሙዚቃ ከልዩ ልዩ ባህላዊ መገለጫዎች ጋር ያቀርባል፡፡

    በአማራ ልማት ማኅበር በተገነባ ማዕከል መድረክ ላይ ያየናቸው የቡድኑ አባላት አንድ ብሔረሰብን ከሚገልጽ አልባሳት ወደ ሌላው ቀይረው በአዲስ ኃይል ወደ መድረኩ ለመመለስ የሚወስድባቸው ጊዜ አጭር ነው፡፡ ለአንድ ምሽት የሚያቀርቧቸውን ብሔረሰቦች ውዝዋዜ ብቻ ሳይሆን የአካባቢውን መገለጫ ባህል በአጫጭር ሙዚቃዊ ተውኔቶች ለማሳየት ይሞክራሉ፡፡ 

    ከወጣቶቹ አንዱ ሀብታሙ መሀመድ ነው፡፡ በእያንዳንዱ ውዝዋዜ ወቅት ፊቱ ላይ ለተወዛዋዥነት ያለውን ፍቅር ማንበብ ይቻላል፡፡ ከአንድ እንቅስቃሴ ወደሌላ እንቅስቃሴ በተዘዋወረ ቁጥር ለሙያው ካለው ፍቅር አሻግሮ ችሎታውን መመልከት ይቻላል፡፡

    ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሐይቅ የተወለደው ሀብታሙ የ22 ዓመት ወጣት ነው፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት የመሰናዶ ትምህርቱን እየተከታተለ በነበረበት ወቅት የኪነት ቡድን አባል መሆን ለሚሹ የተደረገ መጥሪያ ይሰማል፡፡ ልጅ ሳለ አንስቶ ወደ ሙዚቃው ዓለም መቀላቀል ምኞቱ ነበረና ሳያመነታ ጥሪውን ተቀብሎ ተወዳደረ፡፡

    ውድድሩን አልፎ በሥልጠናው ወቅት በየወሩ መገምገሚያ ፈተና የነበረ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው አንስቶ የነበሩትን ዙሮች አልፎ የመጨረሻው ዙር ውስጥ የቡድኑ አባል ከሆኑት ተወዛዋዦች መካከል ተቀላቅሏል፡፡ ሀብታሙ ባህላዊ ውዝዋዜ ሲያቀርብ ሐሴት ቢሰማውም ‹‹የተፈጠርኩበት ወሎን ያህል የምወደው ጭፈራ የለም፤›› ይላል፡፡

    ሀብታሙ ዛሬ የወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን ዳግም መቆርቆር ምክንያት በየዕለቱ በሚወደው ሙያው ውስጥ እንደሚኖር በሀሴት ተሞልቶ ይናገራል፡፡ የታሪካዊው ባህላዊ ቡድን አባል ከመሆን ባሻገር በሙያው የረዥም ዓመታት ዝናን ካተረፉ ባለሙያዎች ጎን መሥራቱና በየዕለቱ የውዝዋዜ ችሎታውን ለማሳደግ ዕድል ማግኘቱ ያስደስተዋል፡፡ የቡድን አጋሮቹ እርስ በርስ ልምድ ከመለዋወጥና ከመተራረም በዘለለ በፍቅር የሚሠሩ መሆኑ ሙያዊ ሕይወቱን ቀና እንዳደረገለትም ይናገራል፡፡

    ወጣቱ ወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን በአካባቢው ባሉ ሰዎች የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህል ከማስተዋወቁም በላይ የቀድሞውን ባህላዊ ቡድን ሕይወት የዘራበትና ደሴን በማስተዋወቅ ረገድ በበጎ እንደሚያነሳቸውም ይናገራል፡፡

    ከአንድ ድምፃዊ ጓደኛው ጋር የሚኖረው ሀብታሙ የባህል ቡድኑ በተለያዩ ቦታዎች የሚደረግለት ጥሪ ያስደስተዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ወደ ጎንደርና ሌሎች አገሮች በመሄድ ያቀረቡትን ዝግጅት በትውስታ የሚያወሳው ሀብታሙ በውዝዋዜ ዝነኛ የሆኑትን እያጣቀሰ ነገ እነሱ የደረሱበት የመድረስ ህልሙን አስረግጦ ይናገራል፡፡

    ሌላው ወጣት ሀዲሴ ገብረማርያም በአዲስ አበባ እምብርት አራት ኪሎ የተወለደ ሲሆን፣ ቡድኑን በባህል ውዝዋዜ ሥልጠና ለማገዝ በሚል ከዓመት በፊት ወደ ደሴ ያቀናል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ የባህል ቤቶች ተወዛዋዥ የነበረው ሀዲሴ የወሎ ላሊበላ ቡድን አባላትን ከተመለከተ በኋላ ጓዙን ጠቅልሎ አዲስ አበባን ተሰናብቶ ደሴ ላይ ከትሟል፡፡ ‹‹አዲስ አበባ ብትናፍቀኝም፤ የወሎ ላሊበላ ባህል ቡድን ፍቅራቸው አሸንፎኛል፤›› የሚለው ሀዲሴ ቡድኑ እንቅስቃሴ የጀመረ ሰሞን አዲስ አበባ መጥተው ለምክር ቤት ያቀረቡትን ዝግጅት ያስታውሳል፡፡

    በባህል ማዕከሉ ውስጥ የሚስረቀረቅ ዜማ ካቀረቡት አንዷ ዓለም ውቤ በወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን ውስጥ ድምፃዊት ናት፡፡ በተወለደችበት አካባቢ የነበረ የገበሬ ማኅበር ኪነት አባል ከመሆን ተነስታ የዚነት ሙሀባን ዘፈኖች ዳግም ተጫውታ አልበም አውጥታለች፡፡ ልጅ እያለች ‹‹መቅደላ›› በተሰኘ የኪነት ቡድን በነበረችበት ወቅት ከወሎ ላሊበላ የኪነት ቡድን ጋር ሙዚቃ እየተዋዋሱ ይጫወቱ ነበር፡፡

    የቀድሞ ወሎ ላሊበላ ቡድን ከፈረሰ በኋላ እሷም ከነበረችበት ቡድን የወጣችው ዓለም፣ ቡድኑ ዳግም በመነሳቱ ደስተኛ መሆኗን ትናገራለች፡፡ በተለይም የወሎን ባህል ከዚያም በላይ የኢትዮጵያን ባህል የማስተዋወቅ ፍላጎት ያላት ዓለም ከቀደሙት ድምፃውያን የማሪቱ ለገሰንና የዚነት ሙሀባን ፈለግ ተከትሎ አልበሞች የማሳተም ህልም አላት፡፡

    ‹‹ሙዚቃ በመዋዋስ የማውቀው ቡድን ዛሬ ጠቅልዬ ገብቻለሁ በምንም የምላቀቅ አይመስለኝም፤›› የምትለው ዓለም፣ በወሎ ላሊበላ የባህል ቡድን የቀድሞው ፍቅርና መተሳሰብን ዛሬ ማግኝቷ ዋጋ የማይከፈልበት መሆኑን ትናገራለች፡፡

    ስለ ባህል ቡድኑ አስተያየታቸውን ከሰጡን ሌላው በኮካ ኮላ ሱፐር ስታርስ ውድድር ላይ ያለፈውን ዙር በአሸናፊነት ያጠናቀቀው ታደሰ መኰንን  ነው፡፡ በደርግ ወቅት በነበረው ወታደራዊ ክፍል ሙዚቃዊ እንቅስቃሴውን አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ፣ በመቀጠልም ወደ ደሴ ተመልሶ ኑሮውንና የሙዚቃ ሕይወቱን በትውልድ አገሩ አድርጓል፡፡

    በቡድኑ በሙዚቀኝነት እንዲሁም በድምፅ በማሠልጠን የሚገኘው ታደሰ እሱ ብቻ ሳይሆን በርካቶች ቡድኑ ከፈረሰ በኋላ ያስቆጫቸው ነበርና የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወደ ተሻለ ደረጃ የማድረስ አቅም የነበረው ባህላዊ ቡድን ለመመለስ ከሙያዊ አጋሮቹ ጋር ጥናት አካሂዷል፡፡

    ታደሰ የባህል ቡድኑ ዳግም መቋቋሙ ተቀዛቅዞ የነበረውን የሙዚቃ መንፈስ የሚያነቃቃ፣ ቱባ ባህል የሚያስተዋውቅ፣ ለአገሪቱ የሚሆኑ ሙዚቀኞችን የሚያፈራ፣ ኅብረተሰቡን የሚያነቃቃ፣ የቱሪዝም ዕድገቱን የሚያነሳሳ ነው ይላል፡፡

    ከምሥራቅ አማራ የተወጣጡ ቢሆንም መላው ኢትዮጵያን የሚወክል ቡድን እንደሆነ የሚናገረው ታደሰ፣ ከሚኖሩበት ማኅበረሰብ አልፎ በመላው ዓለም የኢትዮጵያን ባህል አስተዋዋቂ እንደሚሆኑ ያለውን እምነት ይናገራል፡፡ በዕድሜ የገፉት ለተተኪ የሚሆን ዕውቀት እያስተላለፉ እንዲሁም ወጣት አባላቶች በጥቅም ሳይደለሉ በጥንካሬ የሚንቀሳቀሱበት እንጂ እንደቀድሞው በድንገት ያለምትክ የሚፈርስ እንደማይሆን ያለውን ተስፋም ይናገራል፡፡

    የቡድኑን አባላት የመለመለው፣ የቡድኑ አሠልጣኝ እንዲሁም የቀድሞው ወሎ ላሊበላ ኪነት ቡድን አባል ዳምጤ እንደሚገልጸው ከደብረብርሃን እስከ ሰቆጣ ባለው አካባቢ የሚገኙ ወጣቶች የቀድሞን የኪነት ቡድን ታሳቢ በማድረግ ተሰባስበዋል፡፡

    Read More
    Read more »
RSS