News

  • ተስፋና ሥጋት ያንዣበበበት የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት

    እንደ አገር ከተመሠረተች ገና አራት ዓመት እንኳን ያልሞላት ደቡብ ሱዳን ከአምስት ወራት በፊት በተነሳ የእርስ በርስ ጦርነት ሳቢያ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ዜጐቿ ለስደት ሲዳረጉ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ በእርስ በርስ ግጭቱ ጦስ ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡

    የግጭቱን መንስዔ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በቀድሞው የአገሪቷ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሪክ ማቻር የተቃጣ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ነው በማለት የሚገልጹ ሲሆን፣ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት ግን የምን መፈንቅለ መንግሥት? በማለት ይጠይቃሉ፡፡ 

    በአካባቢው ያሉ አገሮች ኢትዮጵያን ጨምሮ በተናጠልና በኢጋድ አማካይነት የተፈጠረውን ቀውስ በእንጭጩ ለመቅጨት ያደረጉት ጥረት ፍሬ ሳያፈራ ብልጭ ድርግም እያለ እስካለፈው ዓርብ ድረስ ያስመዘገበው ውጤት አልነበረም፡፡ 

    ባለፈው ዓርብ ግንቦት 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ግን የኢጋድ አደራዳሪ ቡድኖችና የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ሁለቱ ወገኖች ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ከአምስት ወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት ተገናኝተው ከመደራደራቸውም ባሻገር፣ ለአምስት ወራት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል የተባለ የሰላም ስምምነትም ፈርመዋል፡፡ 

    ነገር ግን ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊን፣ የሌሎች አገሮችን ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የደቡብ ሱዳን መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይን፣ እንዲሁም የአማፅያኑ ቃል አቀባይን በመጥቀስ የሰላም ስምምነቱ ፊርማ ሳይደርቅና ሃያ አራት ሰዓታት እንኳን ሳይሞላው ሁለቱ ወገኖች ተመልሰው ወደ ጦርነት መግባታቸውን እየዘገቡ ነው፡፡

    የስምምነቱ ይዘት

    የኢጋድ ልዩ ልዑክ በመሆን ሁለቱን ወገኖች ለወራት ሲያደራድሩ በነበሩት የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የአሁኑ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ሥዩም መስፍን የተነበበው የሰላም ስምምነቱ በዋነኛነት ያካተተው፣ በ24 ሰዓት ውስጥ ተፈጻሚ የሚሆን የተኩስ ማቆም ስምምነት፣ የጥላቻ ንግግሮችን ማስወገድ፣ ለዓለም አቀፍ የሰብዓዊ አገልግሎት ድርጅቶች ሥራቸውን ለማቀላጠፍ የሚረዳ መተላለፊያ መፍቀድ፣ የሽግግር መንግሥት ለማቋቋም የሚረዱ ሥራዎችን መሥራትና የተሠሩትን ሥራዎች ለመገምገም ሁለቱ መሪዎች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ዳግም እንዲገናኙ ማድረግ የሚሉ ይገኙበታል፡፡ 

    በሰላም ስምምነቱ ወቅት ሁለቱ መሪዎች በስምምነቱ ተግባራዊነት በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ ቢያረጋግጡም፣ ከስምምነቱ መፈረም በኋላ ከሥፍራው የሚወጡ መረጃዎች ግን ሁለቱም ወገኖች ቃል የገቡለትን ስምምነት በማፍረስ ተመልሰው ወደ ጦርነት መግባታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ 

    Read More
    Read more
  • ሚሸል ኦባማ ከናይጀሪያ ሴቶች ጋር እንደሚቆሙ አስታወቁ

    ናይጀሪያ ውስጥ ቦኮ ሃራም በሚባለው ፅንፈኛ ቡድን የተጠለፉ ወደ 300 የሚጠጉ ልጃገረዶችን ለመፈለግ ለሚደረገው ዓለምአቀፍ ጥረት ድጋፍ ለመስጠት የዩናይትድ ስቴትስ ቀዳሚት እመቤት ሚሼል ኦባማ ሃሽታግ ብሪንግ ባክ አወር ገርልስ (#BringBackOurGirls) - ልጆቻችንን መልሱ የሚል መልዕክት ይዘው የተነሱትን ፎቶግራፍ ትናንት በትዊተር ለቅቀዋል፡፡

    የናይጀሪያ ሴቶች የሴቶች መብቶች ጉዳይ ነው ብለው በሚያምኑት በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ሚስ ኦባማ ያደረጉትና ከጎናቸውም መቆማቸው ልባቸውን የነካው መሆኑን እየገለፁ ነው፡፡

    አንዳንድ የፀጥታ ተንታኞች ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ በጉዳዩ ውስጥ መግባት ከሚኖረው ፋይዳ ይልቅ ጉዳቱ ሊያይል ይችላል የሚል ሥጋት እያሰሙ ነው፡፡

    Read More
    Read more
  • የግብፅ ዕጩ ፕሬዚዳንት ኤል-ሲሲ መነጋገር ይፈልጋሉ

    “የአባይ ውኃ ለግብፅ የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ ነው” ሲሉ የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ዕጩና የቀድሞው የጦር ኃይሎቿ አዛዥ አብደል-ፋታህ ኤል-ሲሲ ተናግረው ከኢትዮጵያ ጋር ግን በመግባባት መሥራት እንደሚያስፈልግ በሁለት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በቀጥታ በተላለፈ ቃለ-ምልልሳቸው ገልፀዋል፡፡

    አንድ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣን ደግሞ የኤል-ሲሲ ንግግር ከቀድሞዎቹ መሪዎች የተለየ ሆኖ እንዳላገኙት ገልፀው ይሁን እንጂ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡና ያሉትን በተግባር ከፈፀሙ “ከግማሽ መንገድ በላይ ሄደን እንቀበላቸዋለን” ሲሉ ለቪኦኤ ማምሻውን አመልክተዋል፡፡ 

    አቶ ፈቅአሕመድ ነጋሽ - በኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዋና ዳይሬክተር


    ቀጣዩ ፕሬዚዳንት ሳይሆኑ አይቀሩም እየተባለ በስፋት የሚወራላቸው አብደል-ፋታህ ኤል-ሲሲ ለፕሬዚዳንትነት እንደሚወዳደሩ ካሳወቁ ወዲህ የመጀሪያውን የቴሌቪዥን ቃለ ምልልስ ላሚስ ኤል ሃዲዲ፣ እንዲሁም ኢብራሂም ኢሣ ከሚባሉ ጋዜጠኞች ጋር አድርገዋል፡፡

    ኤል-ሲሲ ሲቢሲ ከሚባለው የግል ቴሌቪዥን ጣቢያና በተመሣሣይ ጊዜም ኦን-ቲቪ በሚባል ሌላ ጣቢያ በተሠራጨው ረዥም ቃለምልልሳቸው የተነተኑት የመጭ ፖሊሲያቸው ንድፍ የሚመስል ሃሣባቸውን ነው፡፡


    የአባይ ወንዝ፣ የኅዳሴ ግድብና ከኢትዮጵያ ጋር ያሉ ግንኙነቶች ጉዳዮችም ተነስተዋል፡፡

    Read More
    Read more
  • 3 Egyptians caught in Gambella, accused of spying

    GAMBELLA - The regional state government  of Gambella caught today 3 Egyptian nationals who penetrated to the the region via the war torn South Sudan in what the regional government of Ethiopia believed to be a spying mission to find information about the country's  Renaissance Dam. The the three men named as Yusuf Haj, Ismail Azizi and Hassan Garai were caught in separate locations of the region. 
     
    Yusuf went to Abobo on a fake tourist pass to see the Abobo dam of the Abobo county (Woreda). The locals in Abobo worried about the suspicious activities he was making near the dam and that prompted his arrest by the local police. He was then transferred to the regional  administration in Gambella for further investigation and detentions.
     
    The other two were caught at a bus station in Gambella trying to board a bus to Benshangul - Gumuz state without security passes. Benshangul-Gumuz near blue Nile is where the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is located.

    Read More
    Read more
  • Egypt can invade Algeria in three days, Al-Sisi warns

    The Egyptian presidential hopeful, former Minister of Defense and leader of the July 3 military coup Abdel-Fattah Al-Sisi said Thursday that the Egyptian army is capable of invading Algeria "in three days," Algerian media reported.

    According to the Algerian news website Al-Shorouk Online, Sisi told an audience of University teaching staff that the Egyptian army is capable of protecting the western borders against any assault by the so-called Free Egyptian Army.

    "The Egyptian army is strong… before anyone is hurt on the western borders, the army will be there. This is a warning to the Free Army. And if anything happens, I can invade Algeria in three days, if any Egyptian person is harmed," Sisi said.

    Read More
    Read more

Latest Articles

Most Popular